HomeEthiopiaEthiopian NewsThe EmbassyConsular/VisaCommunityTradeInvestmentTourismLinks

Consular/VisasPassport IssuesEthiopian Origin IDCertificate of IdentityLaissez-PasserLegalizationDuty Free Benefits

 

 

ለፓስፖርት የሚቀርቡ ማመልከቻዎች     

 

                                      Click for      አማርኛ        English

 


ማስታወሻ:-

  • ለአዲስ ፓስፖርትም ሆነ ለፓስፖርት እድሳት የሚቀርቡ ማመልከቻዎችም ሆኑ ሌሎች ማናቸውም ሰነዶች እያንዳንዳቸው በሁለት ኮፒ እንዲሆን መደረጉን እንገልፃለን፡፡

  • ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መስፈርቶች በሚገባ ተሟልተው ሲገኙ በህዳርና በታህሳስ ወራት ከስዊድን የሚቀርቡ ፓስፖርት ማመልከቻዎች በ15 ቀን እንዲሁም ከስዊድን ውጭ በ25 ቀን ውስጥ ምላሽ ያገኛሉ፡፡


  1. ለአዲስ ፓስፖርት ለሚቀርብ ማመልከቻ መሟላት የሚገባቸው

1.1.   በአመልካቹ በሚገባ በ2ኮፒ ተሞልቶ የተፈረመ የአዲስ ፓስፖርት ማመልከቻ ቅፅ

1.2.   ከ6 ወር ያልበለጠው 3 ፎቶግራፍ

1.3.   ኢትዮጵያዊ መሆኑን/ዋን የሚያረጋግጥ ሰነድ (original Birth Certificate, Driving license, …ወ.ዘ.ተ) ሰነዱ ከኢትዮጵያ ከመውጣቱ በፊት በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተረጋገጠ መሆን ይኖርበታል፡፡

1.4.    የሌላ ሀገር ሰነድ ያልወሰደ መሆኑን/ዋን ማረጋገጫ ((i.e. Personbevis (Sweden), Folkeregisteret (Denmark), Folkeregister (Norway), Extract from the Population Information System (Finland), Einstaklingar (Island)) ከወጣ ከወር ያልበለጠው ወይም;

1.5.    ከፖሊስ ወይም ከኢሚግሬሽን ባለስልጣን መ/ቤቶች ወይም ከሚመለከተው ሌላ መ/ቤት ምንም አይነት የጉዞ ሰነድ ያልወሰደ/ች ወይም ወስዶ/ዳ የመለሰ/ች መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰነድ፡፡

1.6.      ክፍያ

1.6.1.    415 የስዊድን ክሮነር እንዲሁም

1.6.2.   208 የስዊድን ገንዘብ ለህፃናትና ለተማሪዎች (ተማሪዎች  ከሚማሩበት ተuም በመማር ላይ ያሉ መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ካቀረቡ)

ማስታወሻ- ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተገቢውን የሰነድ ማስረጃ ለማቅረብ ባለመቻል በምስክሮች ለአዲስ ፓስፖርት የሚቀርቡ ማመልከቻዎችን በተመለከተ ከ1.1.3 በስተቀር ከ1.1.1 እስከ 1.1.5 የተጠቀሱት እንደተጠበቁ 3 ምስክሮች;

ሀ. ወቅቱ የላለፈበት (Valid) የኢትዮጵያ ፓስፖርት ወይም ትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ በመያዝ በግንባር ቀርበው ለዚሁ የተዘጋጀውን ፎርም በመሙላት መመስከርና መፈረም ይኖርባቸዋል፡፡

ለ. በግንባር ለመቅረብ ባለመቻል ባሉበት ሀገር Notary Public ወይም ፊርማን ተቀብሎ በሚያረጋግጥ ሌላ አካል የምስክሮች ፊርማ ተረጋግጦ ከፓስፖርት ወይም ትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ኮፒ (Copy Certified) ጋር ተያይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡

ሐ. የምስክሮች የግል ቁጥር (Personal Number); ትክክለኛ የመኖሪያ አድራሻ እንዲሁም የስልክ፤ የፖስታ፤የኢሜይል ወ.ዘ.ተ በግልፅ መገለፅ ይኖርበታል፡፡  የምስክርነት መስጫ ቅፅ (PDF)

2.   በጠፋ ወይም በተበላሸ ፓስፖርት ምትክ እንዲሰጥ ለሚቀርብ ማመልከቻ መሟላት የሚገባቸው

2.1.     በጠፋ ምትክ ለሚቀርብ ማመልከቻ ከቁጥር 1.1.1 እስከ 1.1.4 የተጠቀሱት እንደተጠበቁ ሆኖ

ሀ.  የጠፋው ፓስፖርት ኮፒ ወይም ቁጥር

ለ. የጠፋው ፓስፖርት ከወንጀል ነፃ ለመሆኑ የፖሊስ ወይም የኢሚግሬሽን መረጃ

2.2 በተበላሸ ምትክ ለሚቀርብ ማመልከቻ ከቁጥር 1.1.1 እስከ 1.1.4. የተጠቀሱት እንደተጠበቁ ሆኖ

ሀ.  በተበላሸ ፓስፖርት (ኮፒው መሆን የለበትም)

2.2. ክፍያ

2.2.1.  498 የስዊድን ክሮነር እንዲሁም

 2.2.2.  250 የስዊድን ክሮነር ለህፃናትና ለተማሪዎች (ተማሪዎች ከሚማሩበት ተቋም በመማር ላይ ያሉ የሚገኙ መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ካቀረቡ)

  1. ለፓስፖርት እድሳት ለሚቀርብ ማመልከቻ መሟላት የሚገባቸው

3.1.1.    በአመልካቹ በሚገባ በ2ኮፒ ተሞልቶ የተፈረመ የፓስፖርት እድሳት ማመልከቻ ቅፅ

3.1.2.   የሚታደሰው ፓስፖርት

3.1.3.   ከ6 ወር ያልበለጠው 2 ፎቶግራፍ

3.1.4.   የሌላ ሀገር ሰነድ ያልወሰደ መሆኑን/ዋን ማረጋገጫ ((i.e. Personbevis (Sweden), Folkeregisteret (Denmark), Folkeregister (Norway), Extract from the Population Information System (Finland), Einstaklingar (Island)) ከወጣ ከወር ያልበለጠው ወይም

3.2.        ክፍያ

3.2.1      415 የስዊድን ክሮነር እንዲሁም

3.2.2     208 የስዊድን ገንዘብ ለህፃናትና ለተማሪዎች (ተማሪዎች ከሚማሩበት ተuም በመማር ላይ ያሉ መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ካቀረቡ)

ማስታወሻ:-

ከላይ የተጠቀሱት ማንኛውም ክፍያዎች (Postal Transfer Charge) ወይም (Bank Transfer Charge)ን የሚጨምር አይደለም፡፡ በመሆኑም ከስዊድን በፖስታ ለሚቀርቡ የፓስፖርት ማመልከቻዎች ለ( Postal Transfer Charge) 65 የስዊድን ክሮነር ተጨማሪ ክፍያ መከፈል ያለበት ሲሆን ከስዊድን ውጭ ካሉ ሀገሮች በፖስታ ለሚቀርቡ ማመልከቻዎች ለBank Transfer Charge 60 የስዊድን ክሮነር እና ለPostal Transfer Charge 100 የስዊድን ክሮነር ተጨማሪ መከፈል ይኖርበታል፡፡

ክፍያን በባንክ ቤት መፈፀም ያለበት ክፍያ የተፈፀመበት ደረሰኝ ከማመልከቻው ጋር ተያይዞ መላክ ይኖርበታል፡፡

ማንኛውም ከስዊድን የሚከፈል ክፍያ በ Postgiro No. 629247-8 ፣ እንዲሁም ከስዊድን ውጭ ደግሞ

 

Nordea Bank

IBAN No. SE62 9500 0099 6026 0629 2478, SWIFT-Code NDEASESS, 

OR  Postgiro No. 629247-8. በቅድሚያ መፈፀም ይኖርበታል፡፡

ክፍያን በፖስታ መላክ አይቻልም፡፡


   4. ለህፃናት አዲስ ፓስፖርት መማለት ያለባቸው፤-

  • የአዲስ ፓስፖርት ማመልከቻ ቅፅና 3ፎቶ  (pdf)

  • የህፃን የልደት ወረቀት (ከተወለዱበት ሀገር)

  • የህፃኑ የምዝገባ ሰነድ ፡-(Personbevis (Sweden), Folkeregisteret (Denmark), Folkeregister (Norway), Extract from the Population Information System (Finland), Einstaklingar (Island)) ከወጣ ከወር ያልበለጠው

  • የህፃን ማስመዝገቢያ ቅፅ (በወላጆች ተሞልቶ የተፈረመ)   (pdf)

  • የአባትና እናት ፓስፖርት ኮፒ (Copy Certified) እና

  • የምዝገባ ሰነድ (Family Registration) ፡-(Personbevis (Sweden), Folkeregisteret (Denmark), Folkeregister (Norway), Extract from the Population Information System (Finland), Einstaklingar (Island)) ከወጣ ከወር ያልበለጠው

ማሳሰቢያ

ኤምባሲው ለአገልግሎቱ ከሚጠይቀው የክፍያ መጠን እንዲሁም የባንክ ኮሚሽንና የፖስታ መላኪያ ውጭ የሚፈፀም ማንኛውም በትርፍነት ገቢ የሆነ ገንዘብ የማይመለስ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ተገቢውን ቅድመ ሁኔታ ባለማVላት ወይም ለማVላት ባለመቻል ምንም አይነት የሚሰጥ አገልግሎት አይኖርም፡፡

 

ማሳሰቢያ

ከኢትዮጵያ የሚወጡ (የሚሰጡ) ማንኛውም ሰነዶች ለምሳሌ የልደት የምስክር ወረቀት፤ የጋብቻ የምስክር ወረቀት፤ የትምህርት ማስረጃ፤ የመንጃ ፈቃድ … ወዘተ ከኤምባሲው ለሚጠየቁ አገልግሎቶች እንዲውሉ ከመቅረባቸው በፊት በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተረጋገጡ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

በኤምባሲው ተዘጋጅተው በፖስታ የሚላኩ ማናቸውም ፖስፖርቶች ለማንኛው አገልግሎት ከመዋላቸው በፊት ባለፓስፖርቱ በፓስፖርቱ የመጀመሪያው ገፅ ላይ መፈረም ይኖርበታል፡፡

Denmark, Estonia, Finland, Iceland, Latvia, Lithuania, Norway, Sweden, የሚወጡ (የሚሰጡ) ማንኛውም ሰነዶች ለምሳሌ የልደት የምስክር ወረቀት፤ የጋብቻ የምስክር ወረቀት፤ የትምህርት ማስረጃ፤ የመንጃ ፈቃድ … ወዘተ ከኤምባሲው ለሚጠየቀው አገልግሎት እንዲውሉ ከመቅረባቸው በፊት በየሀገራቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተረጋገጡ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

 

የአዲስ ፓስፖርት ማመልከቻ ቅፅ

New Passport Application Form

 

Postal Address

Embassy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia

P. O. Box 10148

100 55 STOCKHOLM, SWEDEN

 

Fax 46 86609561

 

Telephone

Tel. 46 8 665 60 30

(Consular section) 13:30 -15:30 Hrs.

 

Visiting Address

Embassy of Ethiopia

Löjtnantsgatan 17

115 50 STOCKHOLM

 

9:00 - 12:00 Hrs.(Visiting hours) 

Tel. 46 8 665 60 30

 

የአዲስ ፓስፖርት ማመልከቻ ቅፅ

New Passport Application Form

 

የህፃናት ማስመዝገቢያ ቅፅ

Child Registration Form

 

የአዲስ ፓስፖርት ማመልከቻ ቅፅ

New Passport Application Form

 

ፓስፖርት እድሳት ቅፅ

Passport Renewal application Form

 

 


www.ethemb.se | ©2006 Embassy of FDRE All Rights Reserved | ethemb.all@telia.com

Design by AG