ለፓስፖርት የሚቀርቡ ማመልከቻዎች
ማስታወሻ:-
-
ለአዲስ
ፓስፖርትም ሆነ ለፓስፖርት እድሳት የሚቀርቡ ማመልከቻዎችም ሆኑ ሌሎች ማናቸውም ሰነዶች እያንዳንዳቸው
በሁለት ኮፒ እንዲሆን መደረጉን እንገልፃለን፡፡
-
ከዚህ በታች
የተዘረዘሩት መስፈርቶች በሚገባ ተሟልተው ሲገኙ በህዳርና በታህሳስ ወራት ከስዊድን
የሚቀርቡ
የፓስፖርት
ማመልከቻዎች
በ15 ቀን እንዲሁም ከስዊድን ውጭ በ25 ቀን ውስጥ ምላሽ ያገኛሉ፡፡
-
ለአዲስ ፓስፖርት ለሚቀርብ ማመልከቻ መሟላት
የሚገባቸው
1.1. በአመልካቹ
በሚገባ በ2ኮፒ ተሞልቶ የተፈረመ የአዲስ ፓስፖርት ማመልከቻ ቅፅ
1.2. ከ6
ወር ያልበለጠው 3 ፎቶግራፍ
1.3. ኢትዮጵያዊ
መሆኑን/ዋን የሚያረጋግጥ ሰነድ (original
Birth Certificate, Driving license, …ወ.ዘ.ተ)
ሰነዱ ከኢትዮጵያ ከመውጣቱ በፊት በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ
ሚኒስቴር የተረጋገጠ መሆን ይኖርበታል፡፡
1.4. የሌላ
ሀገር ሰነድ ያልወሰደ መሆኑን/ዋን ማረጋገጫ ((i.e.
Personbevis (Sweden), Folkeregisteret (Denmark),
Folkeregister (Norway), Extract from the Population Information
System (Finland), Einstaklingar (Island))
ከወጣ
ከወር ያልበለጠው ወይም;
1.5. ከፖሊስ
ወይም ከኢሚግሬሽን ባለስልጣን መ/ቤቶች ወይም ከሚመለከተው ሌላ መ/ቤት ምንም አይነት የጉዞ ሰነድ
ያልወሰደ/ች ወይም ወስዶ/ዳ የመለሰ/ች መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰነድ፡፡
1.6.
ክፍያ
1.6.1.
415 የስዊድን ክሮነር እንዲሁም
1.6.2. 208 የስዊድን ገንዘብ ለህፃናትና ለተማሪዎች (ተማሪዎች ከሚማሩበት ተuም
በመማር ላይ ያሉ መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ካቀረቡ)
ማስታወሻ፡-
ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተገቢውን የሰነድ ማስረጃ ለማቅረብ ባለመቻል በምስክሮች ለአዲስ
ፓስፖርት የሚቀርቡ ማመልከቻዎችን በተመለከተ ከ1.1.3 በስተቀር ከ1.1.1 እስከ 1.1.5 የተጠቀሱት
እንደተጠበቁ 3 ምስክሮች;
ሀ.
ወቅቱ የላለፈበት (Valid) የኢትዮጵያ ፓስፖርት ወይም ትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ
ካርድ በመያዝ በግንባር ቀርበው ለዚሁ የተዘጋጀውን ፎርም በመሙላት መመስከርና መፈረም ይኖርባቸዋል፡፡
ለ.
በግንባር ለመቅረብ ባለመቻል ባሉበት ሀገር
Notary Public
ወይም ፊርማን ተቀብሎ
በሚያረጋግጥ ሌላ አካል የምስክሮች ፊርማ ተረጋግጦ ከፓስፖርት ወይም ትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ
ኮፒ (Copy Certified)
ጋር ተያይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
ሐ.
የምስክሮች የግል ቁጥር (Personal
Number);
ትክክለኛ የመኖሪያ አድራሻ እንዲሁም የስልክ፤ የፖስታ፤የኢሜይል ወ.ዘ.ተ በግልፅ መገለፅ ይኖርበታል፡፡
የምስክርነት
መስጫ ቅፅ (PDF)

2. በጠፋ
ወይም በተበላሸ ፓስፖርት ምትክ እንዲሰጥ ለሚቀርብ ማመልከቻ
መሟላት
የሚገባቸው
2.1. በጠፋ
ምትክ ለሚቀርብ ማመልከቻ ከቁጥር 1.1.1 እስከ 1.1.4 የተጠቀሱት እንደተጠበቁ ሆኖ
ሀ. የጠፋው ፓስፖርት ኮፒ ወይም ቁጥር
ለ. የጠፋው ፓስፖርት ከወንጀል ነፃ ለመሆኑ የፖሊስ ወይም የኢሚግሬሽን መረጃ
2.2
በተበላሸ ምትክ ለሚቀርብ ማመልከቻ ከቁጥር 1.1.1 እስከ 1.1.4. የተጠቀሱት እንደተጠበቁ ሆኖ
ሀ. በተበላሸ ፓስፖርት (ኮፒው መሆን የለበትም)
2.2. ክፍያ
2.2.1.
498 የስዊድን ክሮነር እንዲሁም
2.2.2.
250 የስዊድን ክሮነር ለህፃናትና ለተማሪዎች (ተማሪዎች ከሚማሩበት ተቋም
በመማር ላይ ያሉ የሚገኙ መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ካቀረቡ)

-
ለፓስፖርት እድሳት ለሚቀርብ ማመልከቻ መሟላት
የሚገባቸው
3.1.1. በአመልካቹ በሚገባ
በ2ኮፒ ተሞልቶ የተፈረመ
የፓስፖርት እድሳት ማመልከቻ ቅፅ
3.1.2.
የሚታደሰው ፓስፖርት
3.1.3.
ከ6 ወር ያልበለጠው
2 ፎቶግራፍ
3.1.4.
የሌላ ሀገር ሰነድ ያልወሰደ መሆኑን/ዋን
ማረጋገጫ ((i.e.
Personbevis (Sweden), Folkeregisteret (Denmark), Folkeregister
(Norway), Extract from the Population Information System
(Finland), Einstaklingar (Island)) ከወጣ ከወር ያልበለጠው
ወይም
3.2.
ክፍያ
3.2.1
415 የስዊድን ክሮነር እንዲሁም
3.2.2 208 የስዊድን ገንዘብ ለህፃናትና
ለተማሪዎች (ተማሪዎች ከሚማሩበት ተuም
በመማር ላይ ያሉ መሆናቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ካቀረቡ)
ማስታወሻ:-
►
ከላይ የተጠቀሱት ማንኛውም ክፍያዎች
(Postal Transfer Charge)
ወይም (Bank
Transfer Charge)ን
የሚጨምር አይደለም፡፡ በመሆኑም ከስዊድን በፖስታ ለሚቀርቡ የፓስፖርት ማመልከቻዎች ለ( Postal Transfer Charge)
65 የስዊድን ክሮነር
ተጨማሪ ክፍያ መከፈል ያለበት ሲሆን ከስዊድን ውጭ ካሉ
ሀገሮች በፖስታ ለሚቀርቡ ማመልከቻዎች ለBank
Transfer Charge
60 የስዊድን ክሮነር እና ለPostal
Transfer Charge
100 የስዊድን ክሮነር ተጨማሪ መከፈል
ይኖርበታል፡፡
►
ክፍያን በባንክ ቤት መፈፀም ያለበት ክፍያ የተፈፀመበት ደረሰኝ ከማመልከቻው ጋር ተያይዞ መላክ
ይኖርበታል፡፡
►
ማንኛውም ከስዊድን የሚከፈል ክፍያ በ
Postgiro
No. 629247-8
፣ እንዲሁም ከስዊድን ውጭ ደግሞ
Nordea Bank
IBAN
No. SE62 9500 0099 6026 0629 2478, SWIFT-Code NDEASESS,
OR
Postgiro
No. 629247-8. በቅድሚያ መፈፀም ይኖርበታል፡፡
►
ክፍያን በፖስታ መላክ አይቻልም፡፡

4.
ለህፃናት አዲስ ፓስፖርት መማለት ያለባቸው፤-
-
የአዲስ ፓስፖርት ማመልከቻ ቅፅና 3ፎቶ
(pdf)
-
የህፃን የልደት ወረቀት (ከተወለዱበት ሀገር)
-
የህፃኑ
የምዝገባ ሰነድ
፡-(Personbevis
(Sweden), Folkeregisteret (Denmark), Folkeregister (Norway),
Extract from the Population Information System (Finland),
Einstaklingar (Island)) ከወጣ ከወር ያልበለጠው
-
የህፃን ማስመዝገቢያ ቅፅ (በወላጆች ተሞልቶ የተፈረመ)
(pdf)
-
የአባትና እናት ፓስፖርት ኮፒ (Copy
Certified)
እና
-
የምዝገባ ሰነድ
(Family
Registration) ፡-(Personbevis
(Sweden), Folkeregisteret (Denmark), Folkeregister (Norway),
Extract from the Population Information System (Finland),
Einstaklingar (Island)) ከወጣ ከወር ያልበለጠው
ማሳሰቢያ
►
ኤምባሲው ለአገልግሎቱ ከሚጠይቀው የክፍያ መጠን እንዲሁም የባንክ ኮሚሽንና የፖስታ መላኪያ ውጭ
የሚፈፀም ማንኛውም በትርፍነት ገቢ የሆነ ገንዘብ የማይመለስ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
►
ተገቢውን ቅድመ ሁኔታ ባለማVላት
ወይም ለማVላት
ባለመቻል ምንም አይነት የሚሰጥ አገልግሎት አይኖርም፡፡