HomeEthiopiaEthiopian NewsThe EmbassyConsular/VisaCommunityTradeInvestmentTourismLinks

Consular/VisasPassport IssuesEthiopian Origin IDCertificate of IdentityLaissez-PasserLegalizationDuty Free Benefits

 

 

ጥቅምት 2ዐ ቀን 2ዐዐ2 ዓ.ም.

ማስታወቂያ

ቀደም ሲል በውጭ አገር ኖረው ወደ ሀገራቸው ጠቅልለው የሚመለሱ ኢትዮጵያውያንና ትውልድ ኢትዮጵያውያን መኪናን ጨምሮ የቤት ውስጥ መገልገያዎችን ከቀረጥ ነፃ እንዲያስገቡ የሚፈቅድ አሰራር ተግባራዊ ሲደረግ ቢቆይም አንዳንድ ተገልጋዮች የተሰጠውን እድል አለአግባብ በመጠቀማቸው ምክንያት እንዲቆም መደረጉ ይታወሳል፡፡

ይሁን እንጂ የቀረጥ ነጻ እድሉ እንዲቆም ሲደረግ ቀረጥ ከፍሎ ማስገባት የሚቻልበት አሰራር አብሮ የቆመ ባለመሆኑ በውጭ አገር አምስት ዓመትና ከዚያ በላይ ቆይተው ወደ ሀገር ጠቅልለው የሚመለሱ ኢትዮጵያውያን መኪናን ጨምሮ ሙሉ የቤት ውስጥ መገልገያ መሣሪያዎችን ቀረጥ ከፍለው ማስገባት የሚችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ኤምባሲ

ስቶክሆልም

 

 

የግልና የቤት ውስጥ መገልገያ ዕቃዎችን በልዩ መብት በታክስና ቀረጥ ማስገባት ስለሚቻልበት ሁኔታየግልና የቤት ውስጥ መገልገያ ዕቃዎችን በልዩ መብት ከታክስና ከቀረጥ ነፃ ወይም በታክስና ቀረጥ ለማስገባት የባለመብቶቹ አመዳደብና የሚያስገኛቸው የቀረጥ ነፃ መብቶች

በቀረጥና ታክስ ነፃ ተጠቃሚ ለመሆን አመልካቾች ማሟላት የሚጠበቅባቸው መረጃዎች

 

1.   ኢትዮጵያውያን (ቋሚ የመኖሪያ ፍቃድ ያላቸው ወይም ጊዜያዊ የመኖሪያ ፈቃድ ያላቸው ወይም በስደተኛ ካምፕ የሚኖሩ)፣

1.1.  ኦሪጅናል ፓስፖርት

§      ገፅ 1 (ለአዲሱ ፓስፖርት) ወይም ከገጽ 1-7 እና የቅርብ ጊዜ ዕድሣቱን የሚያሳየውን ገጽ ኮፒ (ለድሮው ፓስፖርት)፣

§       ስደተኛ ከሆኑ ከፖሊስ ወይም ከኢሚግሬሽን የተሰጠ የምዝገባ መረጃ፣

§       ተማሪ ከሆኑ ከገጽ 1-7 እና የቅርብ ጊዜ ዕድሣቱን የሚያሳየውን ገጽ እና በፓስፖርቱ ላይ ተማሪነትዎን የሚያሳይ የመኖሪያ ፍቃድ ያለበት ገጽ ኮፒ ሁሉም፣

1.2.  ከሚኖሩበት አገር ከታክስ ባለሥልጣን የቆይታ ጊዜን የሚያሳይ መረጃ፣

1.3.  ተማሪ ከሆኑ ትምህርትዎን ከተከታተሉበት (የትምህርት ዕድል እንደተሰጠዎት የሚያሳይ፣ ትምህርትዎን እንደሚያጠናቅቁ ወይም ማጠናቀቅዎትን የሚገልጽ ሆኖ የጀመሩበትና ያጠናቀቁበትን ጊዜ የሚያሳይ) ማስረጃ፣

1.4. ከኢትዮጵያ በግል የስራ ዕድል አግኝተው የስራ ጊዜዎን ጨርሰው/አቋርጠው የሚመለሱ ከሆነ ከሰሩበት መ/ቤት የሰሩበትን ጊዜ የሚያሳይና ባሉበት አገር ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተረጋገጠ መረጃ፣

1.5.  ጠቅለው የሚመለሱ ከሆነ

§  ጡረተኛ - የጡረታና ከታክስ ባለሥልጣን የቆይታ ጊዜን የሚያሳይ መረጃ፣

§   ሌሎች - ቋሚ የመኖሪያ አድራሻ (Registration of moving abroad) መቀየራቸውን የሚያሳይና ከታክስ ባለሥልጣን የቆይታ ጊዜንና አዲሱን አድራሻ የሚያሳይ መረጃ፣

2.      የኢትዮጵያ ተወላጅ መታወቂያ ካርድ የያዙ

2.1.  ከፓስፖርት ውስጥ ፎቶግራፍ የሚገኝበት ገጽ ኮፒ፣

2.2.  የኢትዮጵያ ተወላጅ መታወቂያ ካርድ ኮፒ፣

2.3.  ጠቅለው የሚመለሱ ከሆነ

§    ጡረተኛ - የጡረታና ከታክስ ባለሥልጣን የቆይታ ጊዜን የሚያሳይ መረጃ፣

§    ሌሎች - ቋሚ የመኖሪያ አድራሻ (Registration of moving abroad) መቀየራቸውን የሚያሳይና ከታክስ ባለሥልጣን የቆይታ ጊዜንና አዲሱን አድራሻ የሚያሳይ መረጃ፣

ማሳሰቢያ:-

v በስዊድን ነዋሪ የሆኑ የሚላክላቸውን የቀረጥና ታክስ ከፍሎ ማስገባት መብት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስችላቸውን ደብዳቤ መላኪያ፣ የመመለሻ አድራሻ የተዘጋጀበት ባለ 65 ክሮነር ስታምፕ የተለጠፈበት የተዘጋጀ ፖስታ አብሮ መላክ፣

v ከስዊድን ውጭ የሚኖሩ የሚላክላቸው የቀረጥና ታክስ ከፍሎ ማስገባት መብት ተጠቃሚ ለመሆን የሚያስችላቸውን ደብዳቤ መላኪያ፣ የመመለሻ አድራሻ የተዘጋጀበት ፖስታና የ1ዐዐ ክሮነር የተመጣጣኝ የሆነ ዋጋ ያለው ኢንተርናሽናል ኩፖን መላክ ይኖርባቸዋል፡፡

The Application Form

 

(pdf)
(jpg)

For further information you may refer to:

Cutstom Authority's Home Page

 

All Consular Services and Requirements

Download Acrobat Reader to see the file in pdf

 

 

 

 

 

 

Postal Address

Embassy of the Federal Democratic Republic of Ethiopia

P. O. Box 10148
100 55 STOCKHOLM, SWEDEN

 

Telephone 004686609166 (Consular section) 13:30 PM - 15:30 PM HRS

Fax: 4686608177

Visiting Address

Embassy of Ethiopia

Löjtnantsgatan 17

115 50 STOCKHOLM

9:00 AM - 12:00 AM (Visiting hours) 

Tel. 46 8 665 60 30

 

E-mail:-

ethemb.consular@telia.com

Fax +46 86609561


www.ethemb.se | ©2006 Embassy of FDRE All Rights Reserved | ethemb.all@telia.com

Design by AG